የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ ሁሉም ተማሪዎች የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እንዲያገኙ አድርጋለች- አምባሳደር መስፍን ቸርነት

By Feven Bishaw

February 21, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ ) ዓለም አቀፍ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ቀን በአዲስ አበባ በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል።

በስነ ስርዓቱ ላይ ተቀማጭነታቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች፣ የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተወካዮች ተገኝተዋል።