የሀገር ውስጥ ዜና

አልማ በአሜሪካ ከሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አባቶችና ምዕመናን ጋር በመተባበር የእለት ደራሽ ምግብና ቁሳቁስ እያሰራጨ ነው

By Feven Bishaw

February 19, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ልማት ማህበር በአሜሪካ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አባቶችና ምዕመናን ጋር በመተባበር በአማራ ክልሉ ጊዚያዊ መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙና በጦርነት ለተጎዱ ወገኖች የእለት ደራሽ ምግብና ቁሳቁስ በማሰራጨት ላይ ነው፡፡

አልማ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሲያትል፣ ዋሽንግተን፣ ኦሪገን አይዳሆ እና አካባቢው ከካሊፎርኒያ የአብያተ- ክርስቲያናት የሀይማኖት አባቶች፣ ምዕመናንና የሀይማኖቱ አገልጋዮች በተገኘ ከ15 ሚሊየን ብር በሚጠጋ ወጪ በደብረ ብርሀን ከተማ ለሚገኙ ተፈናቃዮችና በደቡብና ሰሜን ጎንደር፣ ዋግ ኽምራ፣ ደቡብና ሰሜን ወሎ እንዲሁም በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን በጦርነት ለተጎዱ ወገኖች ነው የዕለት ደራሽ ምግብና የትምህርት ቁሳቁስ በማጓጓዝና በማሰራጨት ላይ የሚገኘው፡፡