የሀገር ውስጥ ዜና

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዶ/ር ከሰተብርሃን አድማሱ ከተመራ የቢግ ዊን ፊላንትሮፒ ቡድን ጋር ተወያዩ

By Feven Bishaw

February 19, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዶ/ር ከሰተብርሃን አድማሱ ከተመራውና በሁሉ አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት የክብካቤ ፕሮግራም ላይ ከሚሰራው የቢግ ዊን ፊላንትሮፒ ቡድን ጋር ተወያዩ፡፡

ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው፥ በሁሉ አቀፍ የቀዳማይ ልጅነት የክብካቤ ፕሮግራም ላይ ከሚሰራው መቀመጫውን ለንደን ያደረገው በዶ/ር ከሰተብርሃን አድማሱ የተመራ የቢግ ዊን ፊላንትሮፒ ቡድን ጋር ተገናኝተን ተወያይተናል ብለዋል።