Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በምዕራብ ወለጋ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ13 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በምዕራብ ወለጋ ጊምቢ ወረዳ መልካ ጋሲ ቀበሌ መልካ ሆላ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ13 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የጊንቢ ወረዳ የትራክ አስተባባሪ ሳጅን ድሪባ ሻንቆ ተናገሩ፡፡
ዛሬ ረፋድ በደረሰው የትራፊክ አደጋ የ13 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን የተናገሩት አስተባባሪው ÷ የሰሌዳ ቁጥሩ 3 ኢት 07550 የሆነ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪ የሰሌዳ ቁጥሩ ኦሮ 54256 በሆነ የህዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪ ላይ በመውጣቱ ነው፡፡
የአደጋው መንስኤም የደረቅ ጭነት ተሸከርካሪው አሽከርካሪ የብቃት ጉድለት መሆኑን ሳጅን ድሪባ ሻንቆ መናገራቸውን ከምዕራብ ወለጋ ዞን ኮሙኒኬሽን ያገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version