Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋትን ለማምጣት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መነሳት ትክክለኛ እርምጃ ነው – ቱርክ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋትን ለማምጣት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መነሳት ትክክለኛ እርምጃ ነው ስትል ቱርክ ገለጸች፡፡
የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ÷ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ መወሰኑን አገሪቱ በበጎ ጎኑ እንደምታየውና እንደምትቀበለው አስታውቋል።
ውሳኔው በኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋትን ለማምጣት የሚያስችል ትክክለኛ እርምጃ እንደሆነ ቱርክ እንደምታምንም ተመላክቷል፡፡
በኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋትን ለማምጣት የሚደረጉ ሁሉንም ጥረቶች መደገፏን እንደምትቀጥልና ለስኬታማነቱም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ትሰራለች ሲል የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version