Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የሳይበር ደኅንነትን ለማስጠበቅ አስቻይ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የሳይበር ደህንነትን ለማስጠበቅ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ከኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡

ፕሮፌሰር ብርሃኑ የኤጀንሲውን የሳይበር ተሰጥዎ ልማት ማዕከል፣ በኤጀንሲው ለምተው በዲጂታል ኤግዚቪሽን ማዕከል የቀረቡ ምርት እና አገልግሎት እንዲሁም የኤጀንሲውን ሠራተኞችና ኃላፊዎችን ቢሮ መጎብኘታቸውን ከኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል ።

ከጉብኝቱ ጎን ለጎን ሚኒስትሩ ከኤጀንሲው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር የተወያዩ ሲሆን፥ የሳይበር ደኅንነትን ለማስጠበቅ በሚያስችሉ የምርምር፣ ልማት እና ስልጠናዎች ላይ በጋራ ለመስራት በሚያስችላቸዉ ጉዳይ ትኩረት አድረገው መክረዋል፡፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version