አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሁሉም የየራሱን አመለካከት ይዞ ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እና ሀገራዊ አንድነት ሊሠራ ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ዑመር እድሪስ ተናገሩ፡፡
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከአዲስ አበባ ከተማ ሙስሊም ወጣቶች እና ሰውነት ይቀድማል በጎ አድራጎት ማኅበር ጋር በመተባበር በደሴ ከተማ በሀገራዊ እና ሃይማኖታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር እያካሄዱ ነው።