የሀገር ውስጥ ዜና

የአርሲ ዞን በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች 18 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር የሚገመት ድጋፍ አደረገ

By Feven Bishaw

February 12, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአርሲ ዞን በምሥራቅ ባሌ ዞን በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች 18 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር የሚገመት የምግብ እህል ድጋፍ አደረገ።

በአርሲ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙሳ ፉሮ የተመራ ቡድን ድጋፉን በጊኒር ከተማ በመገኘት አስረክቧል፡፡