የሀገር ውስጥ ዜና

አካታች ብሔራዊ ምክክሩን ከማሳካት አንፃር የምሁራንን ሚና የሚዳስስ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው

By Feven Bishaw

February 12, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) “አካታች ብሔራዊ ምክክሩን ከማሳካት አንፃር የምሁራን ሚና” በሚል መሪ ሀሳብ የሠላም ሚኒስቴር ከባህርዳር ዩኒቨርሺቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የምክክር መድረክ በባህርዳር እየተካሄደ ነው።

በምክክር መድረኩ የሠላም ሚኒስትር ብናልፍ አንዷለምን ጨምሮ ሚኒስትር ድኤታ ታየ ደንደአ ፣የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የኢንፎርሜሽን እና ስትራቴጅ ኮሙዩኒኬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ዘውዱ እምሩን እና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሠብ እየተሳተፉ መሆኑ ተገልጿል።