Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የዓለም ጤና ድርጅት የመጀመሪያውን 10 ሜትሪክ ቶን የመድሐኒት እና የሕክምና ቁሳቁሶች አቅርቦት መቀሌ አደረሰ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 4፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ጤና ድርጅት ከ33 ነጥብ 5 ሜትሪክ ቶን የመድሐኒት እና የሕክምና ቁሳቁሶች አቅርቦት ውስጥ የመጀመሪያውን 10 ሜትሪክ ቶን ወደ ትግራይ ማድረሱን ገለጸ፡፡

አቅርቦቱ በተባበሩት መንግስታቱ የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ጫኝ አውሮፕላን የሁለት ጊዜ በረራ ወደ ትግራይ ክልል መቀሌ መድረሱንም ነው በኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት በትዊተር ገጹ ያስታወቀው፡፡

በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናትም በተከታታይ በረራዎች ቀሪው አቅርቦት እንደሚሰራጭ ተመልክቷል፡፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version