አዲስ አበባ፣ የካቲት 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ልዩ ስሙ ቻይና ካምፕ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ረፋድ ላይ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር መዋሉን ክፍለ ከተማው አስታውቋል፡፡
የእሳት አደጋው የተነሳው በማህበር ተደራጅተው የእንጨትና ብረት ስራ በሚሰሩ ሼዶች ላይ ነበር።
ከረፋዱ 4፡30 አካባቢ የተነሳው የእሳት አደጋ ከፍተኛ ውድመት ሳያደርስ በህብረተሰቡና በእሳት እና ድንገተኛ አደጋ ባለሙያዎች ርብርብ በቁጥጥር ስር መዋሉን ከክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!