Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ማንኛውም ሰው ፈቃድ ሳይወስድ የበጎ አድራጎት ኮሚቴ በማቋቋም ገንዘብ የማሰባሰብ ስራ እንዳይሰራ ተከለከለ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ማንኛውም ሰው ፈቃድ ሳይወስድ የበጎ አድራጎት ኮሚቴ በማቋቋም ገንዘብ የማሰባሰብ ስራ እንዳይሰራ መከልከሉን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አስታወቀ።

ከዚህ ቀደም ፈቃድ ሳይኖራቸው የበጎ አድራጎት ኮሚቴ አቋቁመው፣ በገንዘብ ማሰባሰብ ላይ የሚገኙ ግለሰቦችና ቡድኖች ከባለስልጣኑ ፈቃድ በመውሰድ ወደ ህጋዊ አሰራር መግባት እንዳለባቸውም አሳስቧል።

ይህንን ተግባራዊ በማያደርጉ አካላት ላይ ተገቢውን ማጣራት በማድረግ አስፈላጊውን ርምጃ እንደሚወስድ ማስጠንቀቁን ኢዜአ ዘግቧል።

ከባለስልጣኑ ፈቃድ ሳይኖራቸው በህዝብ ስም በማንኛውም መንገድ ገንዘብ የማሰባሰብ ስራዎችን መስራት የተከለከለ መሆኑን የገለጸው ባለስልጣኑ÷ በህዝብ ስም የሚሰበሰብ ገንዘብ በህገ ወጥ መንገድ እንዳይባክን የመከላከልና የመጠበቅ ስልጣን እንዳለው አመልክቷል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version