የሀገር ውስጥ ዜና

ሀገራዊ ጥሪን ተቀብለው በሁሉም አውደ-ግንባሮች ሚናቸውን ለተወጡ አካላት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምስጋና አቀረቡ

By Feven Bishaw

February 10, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሀገራዊ ጥሪን ተቀብለው ህይወታቸውን፣ ጉልበታቸውን፣ ሃብታቸውን፣ እውቀታቸውንና ጊዜያቸውን በመስጠት በሁሉም አውደ-ግንባሮች ሚናቸውን ለተወጡ አካላት የአዲስ አበባ አስተዳደርከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምስጋና አቀረቡ።

ከንቲባዋ የአዲስ አበባ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር÷ በደጀንም በግንባርም ከፊት ሆነው በጀግንነት ለመሩት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ለጦር አመራሮች፣ ለጀግናው መከላከያ ሰራዊት አባላትና ለፌደራልና ለክልል ፀጥታ ሀይሎች እንዲሁም ለአማራና ለአፋር ህዝብ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በግማሽ ዓመቱ በተከናወነው ተግባር ለ297 ሺህ 696 ዜጎች የስራ እድል መፍጠር መቻሉንም ገልጸዋል።