የሀገር ውስጥ ዜና

የሱዳን የፖለቲካ ኃይሎች ኢጋድ እንዲያደራድራቸው ፍላጎት አሳይተዋል

By Feven Bishaw

February 06, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሱዳን የፖለቲካ ኃይሎች የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ድርጅት /ኢጋድ/ እንዲያደራድራቸው ፍላጎት ማሳየታቸውን የተቋሙ ዋና ጸኃፊ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ገለጹ።

ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ እየተካሄደ ባለው 35ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ኢጋድ የሱዳንን የፖለቲካ ቀውስ ለመፍታት እያደረገ ያለውን ጥረት አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል።