የሀገር ውስጥ ዜና

አፍሪካን በ2030 የጦር መሳሪያ ድምፅ የማይሰማባት አህጉር የማድረግ አጀንዳ የኅብረቱን መሪዎች አወያየ

By Feven Bishaw

February 06, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አፍሪካን በ2030 የጦር መሳሪያ ድምፅ የማይሰማባት አህጉር የማድረግ አጀንዳ በኅብረቱ የመሪዎች ጉባኤ ተነስቶ ክርክር ተደርገበት።

በኅብረቱ የፖለቲካ፣ የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዲባዮ ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ እንዳሉት፥ በአፍሪካ እየተባባሱ የሚገኙ ኢ-ህገ መንግስታዊ የመንግስት ለውጦች፣ ጽንፈኝነት እና ሽብርተኝነትን ለመከላከል እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ደካማነት አህጉሪቱን የጦር መሳሪያ ድምፅ የማይሰማባት ለማድረግ የተያዘው አጀንዳ ገቢራዊነት መሪዎችን አከራክሯል።