የሀገር ውስጥ ዜና

የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤን ለመዘገብ እስካሁን 340 የውጭ አገራት ጋዜጠኞች አዲስ አበባ ገብተዋል

By Feven Bishaw

February 03, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤን ለመዘገብ እስካሁን 340 የውጭ አገራት ጋዜጠኞች አዲስ አበባ መግባታቸው ተገለፀ።

ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ መከሰት በኋላ መሪዎች ፊት ለፊት ተገናኝተው በሚመክሩበት በአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ በመገኘት የሚዘግቡ 340 የውጭ አገራት ጋዜጠኞች አዲስ አበባ መግባታቸውን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ገልጿል።