የሀገር ውስጥ ዜና

ማዕከሉ አገራዊ የምክክር መድረኩ ተልዕኮ እንዲሳካ መገናኛ ብዙሃን ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል አለ

By Feven Bishaw

January 31, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 23 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ስለ አገራዊ የምክክር መድረኩ ኅብረተሰቡ የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖረውና ተልዕኮው እንዲሳካ መገናኛ ብዙሃን የተዛቡ አመለካከቶችን የሚያጠሩ ስራዎችን ተደራሽ በማድረግ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የሕገ መንግስትና ፌዴራሊዝም አስተምህሮ ማዕከል አስታወቀ።

ማዕከሉ ውይይት በሚሹ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ኅብረተሰቡ የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖረው ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።