አዲስ አበባ፣ ጥር 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ደቡብ ዕዝ፣ ለአባላቱ የሜዳልያ አሰጣጥ መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት በወልድያ ከተማ እያከናወነ ነው።
በመርሃ ግብሩ ላይ የአፋር ክልል ርእሰ መስተዳድር አወል አርባ፣ ምክትል ኤታማዦር ሹም ጀኔራል አበባው ታደሰ፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የሠራዊቱ አባላት መገኘታቸውን አሚኮ ዘግቧል።