የሀገር ውስጥ ዜና

የጠ/ሚ ዐቢይ የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ጉብኝት የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ይበልጥ በሚጠናከርበት ጉዳዮች ላይ ለመምከር ያለመ ነው – የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

By Feven Bishaw

January 30, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ጉብኝት የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ይበልጥ በሚጠናከርበት ጉዳዮች ላይና በቀጣይ በተለያዩ መስኮች የሁለቱ ሀገራት ዘላቂ ጥቅም በሚረጋገጥበት ሁኔታ ላይ ለመምከር ያለመ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካን ቡድናቸው ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት በተባበሩት አረብ ኢምሬትስ፣ አቡ ዳቢ ማቅናታቸው ይታወሳል፡፡