Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በአሸባሪው የህወሓት ቡድን ፆታዊ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች የህግ ከለላ ለመስጠት የተቋቋመው ብሔራዊ ግብረ ኃይል ሥራ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ጥር 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሸባሪው ህወሃት ጾታዊ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች የህግ ከለላ ለመስጠት ብሔራዊ ግብረ ሃይል ተቋቁሞ ወደ ስራ መግባቱን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ተናገሩ።
የጦርነት አስከፊ ገጽታ ከሚበረታባቸው የማህበረሰብ ክፍሎች መካከል በተለይ ሴቶች በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ መሆናቸው ተገልጿል።
አሸባሪው ህወሃት በወረራ በቆየባቸው የአማራና አፋር ክልሎች የተለያዩ አካባቢዎች በሴቶች ላይ የእስገድደዶ መድፈር እና ሌሎች ጭካኔ የተሞላባቸውን ወንጀሎች መፈፀሙን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
Exit mobile version