አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት ከ42 ቢሊየን ብር በላይ ያሰመዘገቡ ባለሐብቶችን በኢንቨስትመንት ዘርፍ ማሰማራት መቻሉን የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለጸ።
የቢሮው የ6 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም በደሴ ከተማ እየተገመገመ ሲሆን ፥ በዚህም ባለፉት 6 ወራት ፈቃድ የወሰዱት የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ሲገቡ ከ87 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎች የሥራ እድል ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል።