የሀገር ውስጥ ዜና

የክልሉ ህዝብ ለሃገራዊ እና ክልላዊ ግብ በጋራ ሊቆም ይገባል- የደቡብ ምዕራብ ህዝቦች ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድር

By Feven Bishaw

January 13, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ምዕራብ ክልል ህዝብ ልዩነትን የሚያሰፉ ጉዳዮችን ወደ ጎን በመተው ለሃገራዊ እና ክልላዊ ግብ በጋራ ሊቆም ይገባል ሲሉ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ወጌሾ ጥሪ አቀረቡ፡፡

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በቤንች ሸኮ ዞን የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን÷ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና አመራሮች ጋር ባደረጉት ውይይትም የክልሉ ህዝብ ከከፋፋይ ሀሳብ ወጥቶ በጋራ መቆም ይኖርበታል ብለዋል፡፡