የሀገር ውስጥ ዜና

የወንጌላውያን ህብረት ለተፈናቀሉ ወገኖች ያሰባሰበውን 10 ሚሊየን ብር አስረከበ

By Feven Bishaw

January 12, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የወንጌላውያን ህብረት ለተፈናቀሉ ወገኖች ያሰባሰበውን 10 ሚሊየን ብር ድጋፍ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስረከበ::

ህብረቱ በጦርነት ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች ከአማኞች የተሰበሰበውን 10 ሚሊየን ብር ነው በዛሬው እለት ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ያስረከበው፡፡