ተጨማሪ 430 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው 1 ሺህ 150 ሰዎች ደግሞ አገግመዋል
አዲስ አበባ፣ ህዳር 23፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ 4 ሺህ 298 የላቦራቶሪ ምርመራ 430 ሰዎች ኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።
በአጠቃላይ እስካሁን ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 110 ሺህ 984 ደርሷል።
እስካሁን ድረስ 76 ሺህ 67 ሰዎች ከቫይረሱ ማገገማቸውን ሚኒስትሯ አስታውቀዋል።
በሌላ በኩል ባለፉት 24 ሰዓታት 1 ሺህ 150 ሰዎች ከቫይረሱ ሲያገግሙ የስድስት ሰዎች ህይወት አልፏል።
ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!