Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮ ጅቡቲ መንገድ 3ኛ የመቆጣጠርያ ኬላ ተከፈተ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የኢትዮ ጅቡቲ መንገድ 3ኛ የመቆጣጠርያ ኬላ ዛሬ አፋር በልሆ ላይ በይፋ ተከፍቷል።
 
የሠላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ወይዘሮ ፍሬአለም ሺባባው÷ ኬላውን በቦታው ተገኝተው መርቀው ከፍተዋል።
 
የኬላው መከፈት በአካባቢው ያለውን ህገወጥ የሰዎች ዝውውርንና ኮትሮባንድን ለመከላከል አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተነግሯል ።
 
በዚሁ ወቅት ወይዘሮ ፍሬዓለም ስራው እንዲሳካ ጥረት ላደረጉ ሠራተኞችና አመራሮች የጅቡቲን መንግስት ጨምሮ ምስጋና ማቅረባቸውን ከሰላም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
 
#FBC
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.