Fana: At a Speed of Life!

4 ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የዓመቱ ምርጥ አትሌት ዕጩ ውስጥ ተካተቱ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ዮሚፍ ቀጀልቻ፣ ታምራት ቶላ፣ ትዕግስት ከተማ እና ሱቱሜ አሰፋ የ2024 ከስታዲየም ውጭ የወንዶች የዓመቱ ምርጥ አትሌት ምርጫ ላይ በዕጩነት ተካተቱ፡፡

አትሌቶቹ በውድድር ዓመቱ በተለያዩ የጎዳና ላይ ውድድሮች ባስመዘገቡት ውጤት ነው ለዕጩነት መካተት የቻሉት።

በውድድር ዓመቱ አትሌት ታምራት ቶላ የኦሊምፒክ እና የበርሊን ማራቶንን ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር ማሸነፉ ይታወሳል፡፡

እንዲሁም አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ በቫሌንሺያ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር የዓለም ክብረ ወሰን በማስመዝገብ ማሸነፉ ይታወቃል፡፡

እንዲሁም በሴቶች አትሌት ትዕግስት ከተማ እና ሱቱሜ አሰፋ በዕጩነት መካተታቸውን የዓለም አትሌቲክስ መረጃ አመላክቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.