Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያና ቻይና ግንኙነታቸውን በማጎልበት ለጋራ ተጠቃሚነት ሊሠሩ ይገባል – ተመራማሪዎች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 15፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና ቻይና ታሪካዊ ግንኙነታቸውን በይበልጥ በማጠናከር ለጋራ ተጠቃሚነት ሊሠሩ እንደሚገባ የአፍሪካ ቻይና ጥናት ተመራማሪዎች አመላከቱ፡፡

የኢትዮጵያና ቻይና ግንኙነት በአክሱም ሥረወ-መንግሥት መጀመሩን እና ከ2 ሺህ ዓመታት በላይ ማስቆጠሩን በዤጂያንግ ኖርማል ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ ጥናቶች ተመራማሪ ዮሮ ዲያሎ (ፕ/ር) ገልጸዋል፡፡

ይህ ዘመናትን ያስቆጠረ ግንኙነት አሁንም ተጠናክሮ መቀጠሉን አንስተው÷ ለአብነትም በመሠረተ-ልማት፣ ትምህርት እና ኢንቨስትመንት ዘርፎች ውጤታማ ሥራ መከናወኑን አብራርተዋል፡፡

በዚሁ ዩኒቨርሲቲ የባህልና ኪነ-ጥበብ ተመራማሪ የሆኑት ታይሊን ሮድሪጎ በበኩላቸው÷ ታሪካዊውን ግንኙነት ለማስቀጠል የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቶችን በይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

አፍሪካና ቻይና በደቡብ ደቡብ ግንኙነታቸው ችግሮቻቸውን በጋራ መፍታትና ትስስራቸውን ሁሉን አቀፍ ማድረግ እንደሚገባቸውም መክረዋል፡፡

በአፈወርቅ እያዩ

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.