Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያና በጀርመን መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የጀርመን መንግሥት ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በጀርመን የኢትዮጵያ አምባሳደር እስክንድር ይርጋ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለጀርመን ፕሬዚዳንት ፍራንክ-ዋልተር ሽታይንማየር አቅርበዋል።

አምባሳደር እስክንድር÷ በሚሲዮኑ በሚኖራቸው ቆይታ ከምዕተ-ዓመት በላይ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ እና የጀርመን ግንኙነት እንዲሁም በተለያዩ መስኮች ያለውን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

በስራ ዘመናቸው ቅድሚያ ሰጥተው የሚሰሩባቸውን መስኮች በመጠቆም ለስኬታማነቱ የጀርመን መንግስትን ድጋፍ መጠየቃቸውን የኤምባሲው መረጃ ያመላክታል፡፡

ፕሬዚዳንት ፍራንክ-ዋልተር በበኩላቸው÷ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የጀርመን መንግሥት ድጋፍ እንደማይለያቸው ለአምባሳደሩ አረጋግጠዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.