ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ ፕሬዚዳንት መሐመድ ዛይድ አልናህያን ጋር ተወያይተዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው÷ የብሪክስ ጉባኤ ከዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ ፕሬዚዳንት ከወንድሜ መሃመድ ዛይድ አልናህያን ጋር የመገናኘት እና የመወያየት እድልም ፈጥሮልናል ብለዋል፡፡