Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ የተሳተፈችበት 16ኛው የብሪክስ ጉባዔ በዝግ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) 16ኛው የብሪክስ ጉባዔ የተጠናከረ የባለ ብዙ ወገን ግንኙነት ለሚዛናዊ የዓለም ልማት እና ደኅንነት በሚል መሪ ሐሳብ በዝግ መካሄዱን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል፡፡

በስብሰባው ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ንግግር አድርገዋል፡፡

ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ 2023 ወደ ብሪክስ እንዲቀላቀሉ ከተጋበዙት ሀገራት መካከል መሆኗ ይታወቃል።

ይህን ተከትሎም ከ2024 ጀምሮ የአባልነቷ እንቅስቃሴ በይፋ መጀመሩን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.