Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ የተመድ ዋና ጸሐፊ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛን አመሰገኑ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 15፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሃና ቴቴህ በቀጣናው ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቀረቡ፡፡

መልዕክተኛዋ በቀጣናው የነበራቸውን የሥራ ጊዜ ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ በፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ ስንብት ተደርጎላቸዋል፡፡

በዚሁ ወቅትም ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ ቀንድ ላበረከቱት ከፍተኛ ድጋፍ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ አመስግነዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.