Fana: At a Speed of Life!

የ”ጋሪ ዎሮ” በዓል በአዲስ አበባ እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 12፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የቦሮ ሺናሻ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “ጋሪ ዎሮ” በዓል በአዲስ አበባ እየተከበረ ነው።

በአከባበር ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በመዲናዋ የሚገኙ የብሔረሰቡ ተወላዶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በሃገር ሽማግሌዎች ምርቃት የተጀመረው ክብረበዓሉ ችቦ በመለኮስ እና በተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች እየተከበረ ይገኛል።

የቦሮ ሺናሻ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “ጋሪ ዎሮ”በመስከረም ወር አጋማሽ የሚከበር በዓል መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

ጋሪ ዎሮ ስለ ህዝቦች አብሮነት ፣ሰላም እና አንድነት የሚነገርበት እንዲሁም ከፈጣሪ ምህረት የሚለመንበት በዓል መሆኑም በዚሁ ወቅት ተገልጿል።

የሺናሻ ብሔረሰብ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከሚገኙ ብሔር ብሔረሰቦች መካከል አንዱ ነው፡፡

በወንድሙ አዱኛ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.