Fana: At a Speed of Life!

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢጋድ የቱሪዝም ሻምፒዮን ሆነው ተመረጡ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የቱሪዝም ሻምፒዮን ሆነው ተመረጡ።

የኢጋድ ፅህፈት ቤት በማህበራዊ ትስስር ገፁ÷ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አዲሱ የኢጋድ የቱሪዝም ሻምፒዮን መሆናውን ስንገልፅ ኩራት ይሰማናል ብሏል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለራዕይ መሪነት በቀጠናው ቱሪዝምን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረውም አስታውቋል፡፡

በተጨማሪም የጠቅላይ ሚኒስትሩ አመራር በኢጋድ አባል ሀገራት ዘንድ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማምጣት፣ ቅርሶችን እና አካባቢን ለመጠበቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያደርግ አስገንዝቧል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.