Fana: At a Speed of Life!

የአዲስ አበባ ከተማ የ2016 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 በጀት ዓመት እቅድና የ2016 በጀት ዓመት የመንግስትና የፓርቲ ሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡

የአስተዳደሩ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ በ2016 በጀት ዓመት ከተያዘው አጠቃላይ እቅድ በአማካይ ከ91 በመቶ በላይ ማሳካት መቻሉን አንስተዋል፡፡

ስኬቶቻችንን በማላቅና በማስፋፋት፣ የጥንካሬዎቻችንን ምንጭ በመለየት እንዲሁም ጉድለቶቻችንን በመሙላት እና በማረም ለኑሮ የተመቸች ውብ ከተማ ለመገንባት የጀመርነውን ሥራ አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉም ገልጸዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.