Fana: At a Speed of Life!

ኮርፖሬሽኑ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 2 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ገቢ አገኘሁ አለ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በተጠናቀቀው የ2016 በጀት ዓመት ከ2 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ አግኝቻለሁ ብሏል፡፡

ከተገኘው አጠቃላይ ገቢም ከ282 ሚሊየን ብር በላይ ትርፍ መሆኑን ነው ኮርፖሬሽኑ የገለጸው፡፡

ገቢው የተገኘውም ለኢንቨስተሮች ከሚቀርቡ በማምረቻ ሼዶችና በለማ መሬት ኪራይ፣ ለመኖሪያ ቤቶች ከሚያገለግሉ አፓርትመንቶች፣ ከሕንጻዎች ኪራይና ለኢንቨስተሮች ከሚቀርቡ የተለያዩ ኢንቨስተር ተኮር የገቢ ማግኛ አገልግሎቶች መሆኑ ተብራርቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.