Fana: At a Speed of Life!

ወደ ፓሪስ ለሚያቀናው የኢትዮጵያ ልዑክ በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት ከነገ በስቲያ ሽኝት ይደረጋል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ ለሚሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን የፊታችን ሰኞ ሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት የክብር ሽኝት እንደሚደረግ ተመላከተ፡፡

በሽኝት ሥነ-ሥርዓቱ ላይም ፕሬዚዳንት ሳኅለወርቅ ዘውዴን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እንደሚገኙ መገለጹን የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡

በዚሁ ወቅትም የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክቶችና የሰንደቅ ዓላማ ርክክብ እንደሚኖር ተጠቁሟል፡፡

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.