ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከፈረንሳይ አምባሳደር ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ጥር 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር ሬሚ ማርሾ ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡
በውይይታቸውም÷ የደጎል አደባባይን መልሶ ማልማት እንዲሁም በመዲናዋ ፈጣን የትራንስፖርት አገልግሎትን በጋራ መስራት ላይ ምክክር ማድረጋቸውን ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ ገልጸዋል፡፡