Fana: At a Speed of Life!

ለሥራ ፈጠራ ሀሳብ ውድድር ምቹ ሥነ-ምህዳር ለመፍጠር ቅንጅታዊ ስራ ይጠይቃል- አቶ ንጉሱ ጥላሁን

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለሥራ ፈጠራ ሀሳብ ውድድር ምቹ ሥነ-ምህዳር ለመፍጠር የዘርፉ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ንጉሱ ጥላሁን ገለጹ፡፡

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የተዘጋጀ ለጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎች ምቹ ስነ-ምህዳር መፍጠርና የብሩህ ኢትዮጵያ 2016 የፈጠራ ሀሳብ ውድድር ላይ ያተኮረ የባለድርሻና አጋር አካላት የምክክር መድረክ ተካሂዷል፡፡

አቶ ንጉሡ ጥላሁን በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት÷ ሚኒስቴሩ ለጀማሪ ሥራ ዕድል ፈጣሪዎችና ኢንተርፕራይዞች ምስረታ ምቹ የሆነ ስነ-ምህዳር ለመፍጠር ሰፋፊ ጥረቶችን እያደረገ ይገኛል፡፡

በዚህም የብሩህ ኢትዮጵን ጨምሮ የተለያዩ ውድድሮችን በየደረጃው ከማካሄድ ባለፈ የማሰልጠን፣ የመሸለምና ተከታትሎ የማብቃት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል፡፡

ለሥራ ፈጠራ ሀሳብ ውድድር ምቹ የሆነ ስነ-ምህዳር ለመፍጠር አስፈፃሚ፣ ባለድርሻ እና አጋር አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ማለታቸውንም የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል ፡፡

በግሉ ዘርፍ ጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎችንና ስታርታፖችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ጀምር ሥራዎች መኖራቸውን ያመሱት አቶ ንጉሡ÷ የከፍተኛ ትምህርት፣ የጥናትና ምርምርና የፋይናንስ ተቋማት በሂደቱ ትልቅ ሚና እንዳላቸው ጠቁመዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.