Fana: At a Speed of Life!

ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር በመሆን ተሾሙ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋን (ፕ/ር) የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር አድርገው ሾሙ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሹመቱን የሰጡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ሆኖ እንዲቋቋም በአዋጅ መጽደቁን ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ለዩኒቨርሲቲው ከተሾሙት ቻንስለር በተጨማሪም አዲስ የቦርድ አመራሮች የተሰየሙለት ሲሆን ቦርዱም ዩኒቨርሲቲውን በሃላፊነት ሊመሩ የሚችሉ ፕሬዚዳንት እና ም/ፕሬዚዳንቶችን በቀጣይነት እንደሚሾም የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.