Fana: At a Speed of Life!

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሥራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሥራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሄደ፡፡

ዛሬ በተካሄደው የስራ ማስጀመሪያ መረሐ ግብር ላይ÷ ለክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

አቶ ጥላሁን ከበደ በመርሐ ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር÷ ወንድማማችነትና መፈቃቃድ ብዙ ርቀት ያስጉዘናል ብለዋል፡፡

ለሕዝቦች አንድነትና እኩል ተጠቃሚነት እንደሚሠሩም ተናግረዋል፡፡

ይህ ክልል እውን እንዲሆን ጠንካራ ትግልና ሕዝበ ውሳኔ ያደረገው ሕዝብም ምስጋና ይገባዋል ነው ያሉት፡፡

በማስተዋል አሰፋ

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.