ብሔራዊ የፀረ-ሙስና አስተባባሪ ኮሚቴ ባከናወናቸው ተግባራት እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ እየተወያየ ነው
አዲስ አበባ፣ የካቲት 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ብሔራዊ የፀረ-ሙስና አስተባባሪ ኮሚቴ እስካሁን ያከናወናቸውን ተግባራት እና የቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ የሚያስችል ግምገማዊ ውይይት እያካሄደ ነው።
ውይይቱ በፌደራል፣ በክልል እና በከተማ መስተዳድር የተቋቋመው የፀረ-ሙስና አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት ነው እየተካሄደ ያለው።
መድረኩ እስካሁን የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት የጋራ ግምገማ ለማካሄድና የቀጣይ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ያለመ መሆኑም ተገልጿል።
በአዲሱ ሙሉነህ