ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሐ ግብር እየተካሔደ ነው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በሐረሪ ክልል እየተካሄደ ነው፡፡
በመርሐ ግብሩ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ፣ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ እንዲሁም ከፍተኛ የፌዴራል እና ክልል መንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ፥ ‘’በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ’’ በሚል መሪ ቃል እየተካሔደ እንደሚገኝ ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!