Fana: At a Speed of Life!

በሽብር ቡድኑ የተጎዱ የምስራቅ አማራ አካባቢዎች የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን ወደ ስራ ለማስገባት ያለመ ውይይት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሽብር ቡድኑ ጉዳት የደረሰባቸውን የምስራቅ አማራ አካባቢዎች የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን ለማነቃቃትና ወደ ስራ ለማስገባት ያለመ ውይይት እየተካሄደ ነው ።
ውይይቱ በክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስተባባሪነት በደሴ ከተማ ነው እየተካሄደ የሚገኘው።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ዶክተር ይልቃል ከፍአለ፣ ባለሀብቶች፣ የዞንና የክልል የስራ ሀላፊዎች እንዲሁም የኢፌዴሪ ኢንዱስትሪ  ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል እና የጠቅላይ ሚንስትሩ የደህንነት አማካሪ አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

በውይይቱ ላይ የደሴ ከተማ ከንቲባ አቶ አበበ ገብረመስቀል፥ በጦርነቱ ወቅት የነበረው መተባበር አሁን በመልሶ ግንባታው ላይ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ዶክተር ይልቃል ከፍአለ በበኩላቸው፥ ክልሉ የትኩረት አቅጣጫውን በተወሰኑ ዘርፎች ላይ በማድረግ እየተንቀሳቀሰ ነው ያሉ ሲሆን፥ በዋናነትም የፀጥታ ዘርፉን ማጠናከር እና በጦርነት ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን አካባቢዎች መልሶ መገንባት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

ኢንቨስትመንትን በማስፋፋትና የልማት ተግባራትን በማጠናከር ይሰራልም ብለዋል።

የውይይት መድረኩ ዋና አላማ በምስራቅ አማራ በጦርነቱ ምክንያት የወደመውን የኢንቨስትመንት ተግባር መመለስ መሆኑንም አንስተዋል።

በጋራ ተናበን በቅንጅት ከሰራን እንደምናሳካው አልጠራጠርም ነው ያሉት።

አዲስ መንፈስ፣ አዲስ የኢንቨስትመንት ስራ ለመፍጠር አሁኑኑ መነሳት አለብን ያሉት ርዕሰ መስተዳደሩ፥ ለዚህም መንግስት የድርሻውን ሀላፊነት ይወጣል ብለዋል።

በይክበር ዓለሙ
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.