Fana: At a Speed of Life!

የኦዲፒ ማእከላዊ ኮሚቴ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ስብሰባውን አጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኦዲፒ) ማዕከላዊ ኮሚቴ በዛሬው እለት ስብሰባውን አጠናቀቀ።

ማእከላዊ ኮሚቴው ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ከተማ ሲያካሂድ የነበረውን ስብሰባ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ማጠናቀቁ ተገልጿል።

ማእከላዊ ኮሚቴው በስብሰባው የፓርቲውን እና የክልሉን መንግስት የስራ አፈፃፀም የገመገመ ሲሆን፥ በወቅታዊ ሀገራዊ እና ክልላዊ ጉዳዮች ላይም ተወያይቷል።

የፓርቲው የውስጥ አንድነት እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ሪፎርምንም እንዲሁም እንደ ሀገር እና እንደ ክልል የተጀመሩ ለውጦች ዙሪያም ምክክር አድርጓል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.