Fana: At a Speed of Life!

ሀገር አቀፍ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ኤግዚቢሽንና ባዛር በሐዋሳ ሊካሄድ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሀገር አቀፍ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ኤግዚቢሽንና ባዛር በሐዋሳ ከተማ እንደሚካሄድ ተገለጸ።

ኤግዚቢሽን እና ባዛሩ “በሀገሬ ምርት እኮራለሁ፤ ከአገር ውስጥ አምራቾች እገዛለሁ” በሚል መሪ ቃል ከጥር 4 እስከ 9 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚካሄድ የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ገልጿል።

በኢንተርፕራይዞች መካከል የእርስ በእርስ የሥራ ትብብር ግንኙነት መፍጠር፣ የገበያ ትስስርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ማመቻቸት የባዛርና ኤግዚቢሽኑ ዓላማዎች እንደሆኑም ነው የተገለጸው፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.