Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

አትሌት ወንድወሰን ከተማ አበረታች መድኃኒት በመጠቀሙ የአራት ዓመት እገዳ ተጣለበት

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 28 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ወንድወሰን ከተማ አበረታች መድኃኒት በመጠቀሙ የአራት ዓመት እገዳ እንደጣለበት የብሔራዊ ፀረ አበረታች ቅመሞች ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። ጽህፈት ቤቱ  አትሌት ወንድወሰን ከተማ ማሞ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ታኅሣሥ 1/2019 በቻይና ሻንዚቢ ዓለም አቀፍ የግል ማራቶን ውድድር ላይ በስፖርት የተከለከለ አበረታች መድኃኒት (ዶፒንግ) መጠቀሙን በመረጋገጡ ለአራት ዓመታት የእግድ ቅጣት ተጥሎበታል ብሏል። አትሌቱ በማንኛውም አገር አቀፍ ይሁን ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ እንዳይሳተፍ ነው…
Read More...

ማንቼስተር ዩናይትድ የኦዲዮን ኢጋሎን ኮንትራት አራዘመ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 24 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ የናይጀሪያዊውን አጥቂ ኦዲዮን ኢጋሎን ኮንትራት ለተጨማሪ ወራት ማራዘሙን አስታወቀ። ክለቡ አጥቂውን እስከ መጭው ጥር ወር ድረስ ለማቆየት መስማማቱን ነው ያስታወቀው። የናይጀሪያዊው የማንቼስተር ዩናይትድ ቆይታ ትናንት አብቅቶ ነበር። የክለቡ አሰልጣኝ ኦሊጉናር ሶልሻዬር የቻይናው ክለብ…

የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ሰኔ 10 ወደ ውድድር ሊመለስ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኮሮናቫይረስ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ሰኔ 10 ቀን ወደ ውድድር ሊመለስ መሆኑ በዛሬው እለት ተገልጿል። ፕሪምየር ሊጉ ማንችስተር ሲቲ ከአርሰናል እንዲሁም አስቶንቪላ ከ ሼፍልድ ዩናይትድ በሚያደርጓቸው ተስተካካይ ጨዋታዎች እንደሚጀምርም ታውቋል። ከዚያ በመቀጠል ከሰኔ 12 እስከ 14 ደግሞ…

ኢትዮጵያዊቷ ሎዛ አበራ በአውሮፓ ሁለተኛ የሊግ ዋንጫ ድሏን አሸነፈች

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 19 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊቷ ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋች ሎዛ አበራ በአውሮፓ ሁለተኛ የሊግ ዋንጫ ድሏን ማሳካት ችላለች። የቀድሞዋ የአዳማ ከተማ ተጫዋች ከዚህ ቀደም በስዊድን የሴቶች ሊግ ከኩንግስባካ ክለብ ጋር የስዊድን የሴቶች የእግር ኳስ ውድድርን በፈረንጆቹ 2018 ማሸነፍ ችላ ነበር። በወቅቱ ለክለቡ ስምንት ጨዋታዎችን…

የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ተጫዋች ተስፋዬ ኡርጌቾ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 5 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ተጫዋች የነበረው ተስፋዬ ኡርጌቾ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ። ከሚኖርበት አሜሪካ ለዕረፍት ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ የነበረው ተስፋዬ ባጋጠመው ድንገተኛ ህመም ህክምና ሲከታተል መቆየቱን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። ፋና ብሮድካስቲንግ…

የ2012 ሁሉም የሊግ ውድድር መሰረዙን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የ2012 ሁሉም የሊግ ውድድር መሰረዙን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በዛሬው እለት አስታወቀ። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በ2012 ሲካሄዱ በነበሩ አጠቃላይ የሊግ ውድድሮች እጣ ፈንታ ላይ በዛሬው እለት በቴሌ ኮንፈረንስ እና በአካል በፌዴሬሽኑ ጽህፈት ቤት ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።…