Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

አትሌት ሳሙኤል ተፈራ በአስታና የ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ሻምፒዮና አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ሳሙኤል ተፈራ በካዛኪስታን አስታና በተካሄደ የ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ሻምፒዮና የአመቱን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አሸንፏል፡፡ አትሌቱ 7 ደቂቃ ከ33 ሴኮንድ ከ85 ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት ነው የዓመቱን የ3 ሺህ ሜትር ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ ማሸነፉን የዓለም አትሌቲክስ መረጃ ያመላከተው፡፡ የ3 ሺህ ሜትር ክብረ ወሰን 7 ደቂቃ ከ26 ሴኮንድ ሲሆን በኬኒያዊው አትሌት ዳንኤል ኮሜን የተያዘ ነው፡፡
Read More...

ታላቁ የወንጪ 10 ኪሎ ሜትር ሩጫ በወንጪ ደንዲ ኢኮ ቱሪዝም ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ታዋቂ አትሌቶች የተሳተፉበት ታላቁ የወንጪ 10 ኪሎ ሜትር ሩጫ በወንጪ ደንዲ ኢኮ ቱሪዝም ተካሄደ፡፡ በውድድሩ በሴቶች ጌጤ አለማየሁ፣ ፎትን ተስፋዬ እና ኑሪት አህመድ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ በቀዳሚነት አጠናቀዋል። በወንዶች ደግሞ አትሌት አዲሱ ነጋሽ፣ ሞገስ ንኡማንና ኤሊያስ ጫኔ ተከታትለው በመግባት…

የአፍሪካ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ይካሄዳሉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽ ሲካሄዱ አንጎላ ከናሚቢያ እንዲሁም ናይጀሪያ ከካሜሩን ይጫዎታሉ፡፡ አንጎላ ከናሚቢያ የሚያደርጉት የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ምሽት 2 ሰዓት ላይ በቡዋኬ ሰታዴ ዴ ላ ፔይክስ ስታዲየም የሚደረግ ሲሆን በጨዋታው አንጎላ የአሸናፊነት ግምት ተሰጥቷታል፡፡ ሁለቱ ቡድኖች በታሪካቸው ካደረጉት…

በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክና አዳማ ከተማ ድል ቀናቸው

አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ12ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ተደርገዋል፡፡ ቀን 9 ሰዓት ላይ በተካሄደ ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባህር ዳር ከተማን 2 ለ 1 በማሸነፍ የሊጉን መሪነት አጠናክሯል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የማሸነፊያ ግቦች ቢንያም ጌታቸውና አዲስ ግደይ ሲያስቆጥሩ÷የባህር ዳር ከተማን…

ታላቁ የወንጪ ሩጫ በነገው ዕለት ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2016 (ኤፍቢ ሲ) የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ያዘጋጀው ውድድር ነገ ማለዳ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራ በሆነው ወንጪ ሐይቅ ዙሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ ይካሄዳል። የአዋቂዎች ውድድር 10 ኪሎ ሜትር እንደሚሸፍን እንዲሁም ህፃናት የሚሳተፉበት የ1 ኪሎ ሜትር ውድድር እንደተዘጋጀ የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ማቴዎስ ሰቦቃ…

የርገን ክሎፕ የ2023/24 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሲጠናቀቅ ከሊቨርፑል ይሰናበታሉ- ክለቡ

አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሊቨርፑሉ አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ከክለቡ የ2023/24 እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር መርሐ-ግብር ሲጠናቀቅ ከክለቡ እንደሚሰናበቱ ተሰምቷል፡፡ የተጀመረው የፕሪሚየር ሊግ ውድድር መርሐ-ግብር እስከሚጠነቀቅ ድረስ በአሰልጣኝነታቸው እንደሚቀጥሉም ተገልጿል፡፡ የመርሲሳይዱ ክልብ ሊቨርፑል አሁን ላይ የእንግሊዝ ፕሪሚየር…

የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀቁ

አዲስ አበባ፣ ጥር 16፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ12ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ተደርገዋል፡፡ ቀን 9 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ መድን እና ሻሸመኔ ከተማ ያካሄዱት ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡ የኢትዮጵያ መድንን ብቸኛ ግብ ወገኔ ገዛኸኝ ሲያስቆጥር÷ የሻሸመኔ ከተማን ደግሞ አብዱልቃድር ናስር አስቆጥሯል፡፡…