Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ ሀገር-በቀል ኢኮኖሚ ላይ በትኩረት እንደምትሠራ ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)ኢትዮጵያ ሀገር-በቀል ኢኮኖሚ ላይ በትኩረት እንደምትሠራ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ አስታወቁ።

ሚኒስትሩ “ከዕዳ መውጣት ፣ ዕድገት ማስመዝገብ” በሚል መሪ ቃል አሜሪካ በተዘጋጀው በዓለም አቀፉ የኢኮኖሚ መድረክ የፓናል ውይይት ላይ ተሳትፈዋል።

ዓለም ባንክ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም እንዲሁም የግሉ ዘርፍ የፋይናንስ ተዋንያን እና ሌሎች የገንዘብ ተቋማት ኢትዮጵያ የምንዛሬ አቅርቦት ዕጥረቷን ለመፍታት የምታደርገውን ጥረት እንዲደግፉ ጠይቀዋል፡፡

በጉባዔው ከዓለም ባንክ በተጨማሪ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም እንደተካፈለም ተጠቁሟል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.