ሩዋንዳ ከአስከፊው የዘር እልቂት በኋላ ዳግም እንድትገነባ ኢትዮጵያ ላበረከተችው አስተዋጽኦ ምስጋና አቀረበች
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩዋንዳ ገጥሟት ከነበረው አስከፊው የዘር እልቂት በኋላ ዳግም እንድትገነባ ኢትዮጵያ ላበረከተችው አስተዋጽኦ ምስጋና አቀረበች።
በሩዋንዳ ኪጋሊ የሩዋንዳ ዘር ጭፍጨፋ 30ኛ ዓመት ዛሬ ታስቧል።
በመታሰቢያ ስነ-ስርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሌሎች ሀገራት መሪዎች ተገኝተዋል።
የሩዋንዳ ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር የኢትዮጵያ ህዝብ እና መንግስት ሩዋንዳውያን በችግር በነበሩበት ወቅት ላሳዩት አብሮነት አመስግነዋል።
በተለይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በወጣትነት እድሜያቸው የሰላም አስከባሪ በመሆን ሩዋንዳ የዘመቱ መሆናቸውን አንስተው አመስግነዋል።
በአልዓዛር ታደለ